Ethiopian Folktales

The Twin Brothersመንትዮቹ ወንድማማቾች

Oromiaኦሮሚያ

Text size Share

Narrated by Moti Wayeesa

Once upon a time, there was a husband and wife, and the wife became pregnant. So the husband began slaughtering many sheep and feeding them to her, so that she would become strong.

Very soon nine months had almost gone by. So the husband prayed to God and said, “Dear God, please keep the baby in my wife’s stomach a bit longer so she can eat more and become stronger.”

So, as God hears all prayers, the child stayed in the wife’s stomach. And in the meantime the husband continued living with his wife and she became pregnant for the second time, while the first child was still in her womb.

So after a period of nine months, she gave birth to two boys. In fact, they were twins but one was much older than the other, because he had stayed in his mother’s womb for such a long time.

Anyway, the twins were born and they grew up. And after some time the man and his wife died and the sons had to decide who should take the inheritance.

The older one said, “I am older, so I should take it.”

But the younger one said, “No, we were born at the same time, so you are no older than I am."

They went to the elders and the elders found this a very difficult case.

So they took them to a large lake and they said, “We cannot decide this, therefore what we’ve got to do is to let God decide it. We’ve talked to Abba Gedda, and the solution is that you’ve got to dive to the bottom of the lake and come up with whatever you find at the bottom.”

The brothers agreed and they both jumped in. After some time the younger one came up with a fish in his hand. But the second one came out with a keleche (an Oromo ritual object) in his hand. And this is how the Oromo people explain how they got the keleche. And they say that because of this, the elder sons have always been given the keleche instead of the younger ones.

መንትዮቹ ወንድማማቾች

በሞቱ ወዬሳ የተተረከ

በአንድ ወቅት አብረው የሚኖሩ ባልና ሚስት ነበሩ፡፡ ሚስትየውም ባረገዘች ጊዜ ጠንካራ ትሆን ዘንድ ብዙ በጎችን እያረደ ያበላት ነበር፡፡

ጊዜው በጣም ሄዶ ዘጠኝ ወር ደረሰ፡፡ ባልየውም ለፈጣሪ እንዲህ እያለ ፀለየ “አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ተጨማሪ ምግብ በልታ እስክትጠነክር ድረስ ህፃኑን በማህፀኗ ውስጥ ትንሽ አቆየው፡፡”

እናም አምላክ የሁሉንም ፀሎት ይሰማልና ህፃኑ በእናቱ ማህፀን ውስጥ ቆየ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ባልየው ከሚስቱ ጋር መኖሩን ስለቀጠለ ያረገዘችውን ህፃን ሳትወልድ በድጋሚ ሌላ ልጅ አረገዘች፡፡

እናም ከዘጠኝ ወራት በላይ በነፍሰጡርነት ከቆየች በኋላ መንትያ ልጆች ወለደች፡፡ ሆኖም አንደኛው ህፃን ግን በእናቱ ማህፀን ውስጥ ለረጅም ጊዜ በመቆየቱ ከሁለተኛው ህፃን በእድሜ በጣም ይበልጥ ነበር፡፡

የሆነው ሆኖ መንትዮቹ ተወልደው አብረው አደጉ፡፡ ከጊዜ በኋላም እናትየው ስትሞት ልጆቹ ወራሽ የትኛቸው መሆን እንዳለበት መወሰን ነበረባቸው፡፡

ታላቅየውም ልጅ “እኔ ታላቅ ስለሆንኩ ውርሱ የሚገባኝ እኔ ነኝ፡፡” አለ፡፡ ታናሽየው ልጅ ግን “የተወለድነው በአንድ ጊዜ በመሆኑ አንተ ከእኔ በእድሜ አትበልጥም፡፡” አለው፡፡

ከዚያም ወደ አገር ሽማግሌዎች ሄደው ሽማግሌዎቹ ጉዳዩን ለመዳኘት ተቸገሩ፡፡ ስለዘህ ልጆቹን ወደ አንድ ሃይቅ ወስደው “ይህንን ጉዳይ እኛ መዳኘት አንችልምና ውሳኔውን ለፈጣሪ ነው መተው ያለብን፡፡” አሉ፡፡ በጉዳዩም ላይ አባገዳን ያማከርን ሲሆን መፍትሄውም ሁለታችሁም ወደ ሃይቁ ወለል ወርዳችሁ ያገኛችሁትን ነገር ይዛችሁ ትወጣላችሁ፡፡” አሏቸው፡፡

መንትዮቹም በዚህ ተስማምተው ወደ ሃይቁ ውስጥ ዘለው ገቡ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ታናሹ ወንድም ዓሣ ይዞ ሲወጣ ታላቅየው ደግሞ ከለቼ በእጁ ይዞ ወጣ፡፡ የኦሮሞ ብሔር አባላት ከለቼን በዚሁ ሁኔታ እንዳገኙ ይናገራሉ፡፡ እናም በዚህ ምክንያት ነው የብሔሩ የበኩር ልጆች ከታናናሾቹ ይልቅ ከለቼው የሚሰጣቸው፡፡

In the original voice — hear tales from Oromiaኦሮሚያ, told in Afaan Oromo. Listen ›