Ethiopian Folktales

The Sheep and the Goatበግና ፍየል

Tigrayትግራይ

Text size Share

Narrator Unknown

A sheep and a goat were eating grass in a field.

The sheep said to the goat, “Let’s go home.”

The goat said, “Why? I want to eat more.”

The sheep felt cold and said, “Why don’t I go to the cave?”

Finally the sheep went to the fox’s den to keep warm.

And the hare came and said, “Who is in the fox’s den?”

The sheep says, “It’s me, who butts with my head anyone who comes across me.”

The hare was afraid. She went away.

The hyena came and said, “Who is it in the fox’s den?”

The sheep said again, “I am the one who butts with my head anyone who come across me.”

And the hyena also ran away.

The fox came and asked the same question, but ran away when the sheep gave the same answer.

The fox asked the hyena what she should do.

He told her, “Just go to the den and call, “Sheep! Can I be your maid?”

So the fox went and asked her, “Can I come in and be your maid?”

The sheep said, “OK.”

So the fox went in and killed it.

በግና ፍየል

ተራኪው የማይታወቅ

አንዲት በግና አንዲት ፍየል መስኩ ላይ ሳር ይግጡ ነበር፡፡ በጓም ፍየሏን “ወደቤታችን እንሂድ፡፡” አለቻት፡፡
ፍየሏ ግን “ለምን? እኔ መጋጥ እፈልጋለሁ፡፡” አለቻት፡፡ በጓ ግን ስለበረዳት “ዋሻው ውስጥ ለምን አልገባም?” ብላ ወደ አንዲት ቀበሮ ዋሻ ገብታ መሞቅ ጀመረች፡፡

በዚህ ግዜ አንዲት ጥንቸል መጥታ “በቀበሮዋ ቤት ውስጥ ያለው ማነው?” ብላ ስትጠይቅ በጓም እኔ የተጠጋኝን ሁሉ በጭንቅላቴ የምመታው በግ ነኝ፡፡”  አለች፡፡

ጥንቸሏም ፈርታ ሄደች፡፡

ጅቡም መጥቶ “በቀበሮዋ ቤት ውስጥ ያለው ማነው?” ሲል አሁንም በጓ “እኔ የተጠጋኝን ሁሉ በጭንቅላቴ የምመታው በግ ነኝ፡፡” አለችው፡፡ ጅቡም ፈርቶ ሸሸ፡፡

ቀበሮዋም መጥታ ተመሳሳይ ጥያቄ ስትጠይቅ በጓም ተመሳሳይ መልስ ስለሰጠቻት ሮጣ ተመለሰች፡፡ ከዚያም ቀበሮዋ ጅቡን ምን ማድረግ እንዳለባት ስትጠይቀው ጅቡም “ወደ ዋሻው ሄደሽ ‘በግ ሆይ፣ ገረድሽ መሆን እችላለሁ’ በያት አላት፡፡ ቀበሮዋም እንደተባለችው ሄዳ በጓን “ገብቼ ገረድሽ ልሁን?” ብላ ስትጠይቃት በጓም “እሺ” ብላ ስትከፍት ቀበሮዋ ገብታ ገደለቻት፡፡