Ethiopian Folktales

The Mercy of Haile Selassieየኃይለሥላሴ ምህረት

Amharaአማራ

Text size Share

Narrated by Worku Mersha

There was somebody living in a small village called Mota.

He used to say without reason, “I will be king one day! I will be king one day!” time and again.

So he was brought to the Emperor’s court.

His Majesty said, “Why have you brought this man here?”

They replied, “Because he always says he’s going to be a king, without having any royal blood.”

The Emperor replied, “Did he collect a crowd and tell them this? Did he agitate?”

“No,” they said.

“Then release him,” said Haile Selassie. “No one can prevent wishes.”

የኃይለሥላሴ ምህረት

በወርቁ መርሻ የተተረከ

ሞጣ ከምትባል አንዲት መንደር ውስጥ የሚኖር ሰው ነበር፡፡ ሰውየውም ያለምንም ምክንያት “አንድ ቀን ንጉስ እሆናለሁ! አንድ ቀን ንጉሥ እሆናለሁ!” እያለ ደጋግሞ ይናገር ነበር፡፡

በዚህም ምክንያት ወደ ንጉሡ ዘንድ ለፍርድ ቀረበ፡፡ ንጉሡም “ይህንን ሰው ለምንድነው ያመጣችሁት?” ብለው በጠየቁ ጊዜ ሰዎቹም “ምንም ንጉሣዊ ደም ሳይኖረው አንድ ቀን ንጉሥ እንደሚሆን ይናገራል፡፡” ብለው ከሰሱት፡፡

ንጉሡም “ህዝቡን ሰብስቦ ነው ይህንን የተናገረው? ቅስቀሣስ አድርጓል?” ብለው ሲጠይቁ ሰዎቹ “አላደረገም::” ብለው መለሱ፡፡ “በሉ ልቀቁት” አሉ ኃይለሥላሴ “የሰውን ምኞት መግታት አይቻልም፡፡”

In the original voice — hear tales from Amharaአማራ, told in Amharic. Listen ›