The Mourning of the Hyenasየጅቦች ሃዘን
Amharaአማራ
Narrated by Yirga Ejigu
Once one of the sons of the hyenas died and all the hyenas were gathered for mourning.
The news came to the ears of the donkey and the donkey said, “Why don’t we go and join them? If we do, they will stop eating us.”
The others said, “It’s a good occasion to make friends, so let’s go.”
They all agreed and went to the hyena’s house.
The hyenas saw the donkeys from a distance and said, “Who are these animals coming to us?”
The other replied, “I think they are donkeys. How dare they come to our house?”
All were surprised and the donkeys came right into the house and the leader said, “Even if you eat something black, the hyena’s shit is white. What has touched the son of my lord?”
The hyena replied, “Whatever you may say will not come into my heart. What shall hyenas eat now when they are hungry?”
And all the donkeys were worried and started looking at each other.
One whispered, “We’d better run away.”
The other replied, “No, we’re already in their hands.”
“So what shall we do?”
“Let’s give them our lips and let them eat that.”
They agreed, and their leader reported this to the hyenas. The hyenas all jumped on to the donkeys and tore away their lips, so they faced each other in two lines.
Therefore the donkeys were lipless and looked as if they were smiling and a hyena said, “How can you laugh at us now that our son is dead? You came to mock us.”
So they jumped on the donkeys and ate them.
So from that time on it was said, “Ai-ya Hyena, (Father Hyena), please eat me," when stating false reasons.
የጅቦች ሃዘን
በይርጋ እጅጉ የተተረከ
በአንድ ወቅት አንድ የጅቦች ልጅ ሞቶ ጅቦች ሁሉ ሃዘን ተቀምጠው ነበር፡፡ ይህም ዜና ከአህዮች ጆሮ ደርሶ ነበርና አንድ አህያ እንዲህ አለ “ለምን ለቅሶ አንደርሳቸውም? ይህንንም ካደረግን እኛን ማደን ይተዋሉ፡፡”
ሌሎቹም እንዲህ አሉ “ከጅቦቹ ጋር ወዳጅነት ለመመስረት ይህ መልካም አጋጣሚ ነው፡፡ ስለዚህ እንሂድ::” ብለው ተስማምተው ወደ ጅቡ ቤት አቀኑ፡፡
ጅቦቹም አህዮቹን በሩቅ ባዩ ጊዜ “እነዚያ ወደእኛ የሚመጡት እንስሳት እነማን ናቸው?” ብለው ጠየቁ፡፡ ሁሉም በመገረም እያዩአቸው ሳለ አህዮቹ በቀጥታ ወደ ጅቡ ቤት ገቡ፡፡ ያህዮቹም መሪ እንዲህ አለ “የምትበሉት ነገር ጥቁር እንኳን ቢሆን የጅብ ፋንድያ ነጭ ነው፡፡ የጌታዬን ልጅ ምን አገኘው?” ጅቡም እንዲህ ብሎ መለሰ “ምንም ብትለኝ አይገባኝም፡፡ አሁን ጅቦቹ ሁሉ ተርበዋልና ምን ይበላሉ?”
አህዮቹም ሁሉ በጭንቀት እርስ በእርስ መተያየት ጀመሩ፡፡ አንደኛውም “ብናመልጥ ይሻላል” ብሎ በለሆሳስ ተናገረ፡፡ “ሌላኛው ግን አሁንማ በእጃቸው ውስጥ ነው ያለነው፡፡” አለ፡፡
“ታዲያ ምን ብናደርግ ይሻለናል?”
“ከንፈራችንን እንስጣቸውና ያንን ይብሉ::”
በዚህም ተስማምተው አለቃቸው ይህንኑ ለጅቦቹ አስረዳ ጅቦቹም በሙሉ ወደ እህዮቹ ዘለው ከንፈሮቻቸውን በጭቀው ጥለው በሁለት ጎራ ተፋጠጡ፡፡
ስለዚህ አህዮቹ ከንፈር ስለሌላቸው በጅቦቹ የሚስቁ ይመስል ስለነበር አንዱ ጅብ “ልጃችን ሞቶ እያለ እንዴት ነው የምትስቁብን? ልታሾፉብን ነው የመጣችሁት? አለ፡፡
በዚህም ጊዜ ጅቦቹ በሙሉ ዘለው አህዮቹን ይዘው በሏቸው፡፡
ከዚያን ጊዜ አንስቶ አያ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ ይባል ጀመር፡፡
In the original voice — hear tales from Amharaአማራ, told in Amharic. Listen ›