Ethiopian Folktales

Bullets, Let Alone Ballsእንኳን ከኳስ ከጥፋትም

Amharaአማራ

Text size Share

Narrated by Daniel Legesse

Once upon a time, Emperor Haile Selassie and President Jomo Kenyatta of Kenya were watching the football match between their national teams. The game was over without scoring goals by either team. Finally the referee decided that the two emperors would act as goalkeeper.

First Jomo Kenyatta acted as goalkeeper and the Ethiopian Emperor as the person who kicked a penalty. And the Ethiopian Emperor scored a goal. Now it was the Kenyan Emperor’s turn and the Ethiopian Emperor to be goalkeeper.

The Kenyan Emperor started running from the other goal all the way down the field to build up his speed and the Ethiopian Emperor was afraid and ran away and the Kenyan Emperor scored.

Haile Selassie was asked, “Why did you run away?”

“We Ethiopians save ourselves from bullets, let alone balls.”

እንኳን ከኳስ ከጥፋትም

በዳንኤል ገሠሠ የተተረከ

ከዕለታት አንድ ቀን አፄ ኃይለሥላሴና የኬንያው ፕሬዝደንት ጆሞ ኬንያታ የአገሮቻቸው ብሔራዊ ቡድኖች የእግር ኳስ ግጥሚያ ሲያደርጉ ይመለከቱ ነበር፡፡ ታዲያ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ጨዋታው ይጠናቀቃል፡፡ በመጨረሻም የጨዋታው ዳኛ ሁለቱ መሪዎች እንደ ግብ ጠባቂ ሆነው ጨዋታው ይዳኛል ብለው ወሰኑ፡፡

በዚህም መሠረት በመጀመሪያ ጆሞ ኬንያታ ግብ ጠባቂ ሆነው የኢትዮጵያው ንጉስ ፍፁም ቅጣት ምት በመምታት ጎል አስቆጠሩ፡፡

ቀጥሎ ፍፁም ቅጣት ምት መምታቱ የኬንያው ፕሬዝደንት ተራ ስለነበር የኢትዮጵያው ንጉሥ ጎል ጠባቂ ሆኑ፡፡

እናም የኬንያው መሪ ኳሱን ለመምታት ከሌላኛው የግብ ክልል ተነስተው ሜዳውን ሙሉ ሲንደረደሩ ባዩ ጊዜ የኢትዮጵያው ንጉሥ ግቡን ትተው ስለሸሹ የኬንያው መሪ ግብ ያስቆጥራሉ፡፡

ኃይለሥላሴም “ለምንድነው የሸሹት?” ተብለው ሲጠየቁ “እኛ ኢትዮጵያውያን እንኳን ከኳስ ከጥይትም እናመልጣለን፡፡” ብለው መለሱ ይባላል፡፡

In the original voice — hear tales from Amharaአማራ, told in Amharic. Listen ›