The Dog’s Tailየውሻው ጅራት
Omo Zoneኦሞ ዞን
Narrated by Oesha Tushklo
The donkey and the dog ran away from their master’s house because they were treated very badly and they went to live together in another place. On reaching green grassland the donkey ate so much that he couldn’t resist braying.
“Can I bray?” he asked the dog.
“No, the hyena will come and eat you. “
But the donkey couldn’t resist and he brayed three or four times.
“Well, if you want to bray, I’ll hide and see what will happen to you.”
The dog sat on a rock to see what would happen. The hyena came when he heard the donkey bray, and killed him, and put the meat beneath a rock.
The dog saw the fresh meat and he began to salivate. His mouth watered. The hyena looked up because the saliva fell on him and he saw the dog. The hyena ordered the dog to come out of the tree and skin the donkey.
The dog came down and after skinning the donkey, he saw the heart and he couldn’t resist it. His mouth watered so much he couldn’t stop himself and he snatched the heart and ate it.
When the hyena checked whether the whole body was there, he couldn’t see the heart.
“Where is the heart?” he asked the dog.
“The donkey doesn’t have a heart. If he had one, he wouldn’t have brayed to attract you.”
The dog knew now that the hyena wanted to kill him and so he ran. The hyena chased him and when he saw a thorny kind of fence the dog shot through the thorns. His whole body was through except the tail, which the hyena snatched and bit off. The thorny fence surrounded the compound of his master.
So the hyena said proudly, “You have escaped, but I have cut off your tail.”
But the dog laughed at the hyena.
“My master sleeps on a dried hide. I sleep next to him. He was going to cut off my tail anyway one of these days so that I wouldn’t scatter the ashes over him as he sleeps, as is usual for us dogs. So don’t feel triumphant. It would have happened anyway.”
የውሻው ጅራት
በኦዬሻ ቱሽክሎ የተተረከ
በጌታቸው በጣም ይበደሉ የነበሩ አንድ አህያና አንድ ውሻ ጠፍተው ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ለመኖር በማሰብ ከቤታቸው ወጥተው ሄዱ፡፡ ከአንድ ለምለም ስፍራ በደረሱም ጊዜ አህያው እስኪጠግብ ስለበላ ማናፋት አማረውና ውሻውን “ማናፋት እችላለሁ?” ብሎ ጠየቀው፡፡
ውሻውም “ተው! ጅብ የሰማ እንደሆን መጥቶ ይበላሃል፡፡” ቢለውም አህያው ከጥጋቡ የተነሳ ራሱን መግዛት ተስኖት ሶስት ወይም አራት ጊዜያት አናፋ፡፡
በዚህ ጊዜ ውሻው “እንግዲያው አንተ ማናፋት ካማረህ እኔ ተደብቄ የሚሆነውን አያለሁ፡፡” ብሎ ከአንድ አለት ላይ ወጥቶ ምን እንደሚከሰት መከታተል ጀመረ፡፡ ጅቡም የአህያውን ማናፋት ሰምቶ በመምጣት ገድሎት ስጋውን ከአለቱ ስር አስቀመጠ፡፡
ትኩሱን ስጋ ያየውም ውሻ ምራቁን ማዝረክረክ ጀመረ፡፡ በዚህ ጊዜ የውሻው ምራቅ ጠብ ያለበት ጅብ ቀና ብሎ ሲመለከት ውሻውን አየው፡፡ ከዚያም ጅቡ ውሻው ከተደበቀበት ወርዶ የአህያውን ቆዳ እንዲገፍ አዘዘው፡፡
ውሻውም ካለበት ቦታ ወርዶ አህያውን ከገፈፈው በኋላ የአህያውን ልብ ሲያይ መታገስ ስላልቻለና በመጎምዠት አፉን ምራቅ ስለሞላው የአህያውን ልብ ለቀም አድርጎ ዋጠው፡፡ ጅቡም የአህያው ሙሉ አካላት እንዳለ ሊፈትሽ ሲመጣ ልቡን ያጣውና ውሻውን “ልቡ የታለ?” ብሎ ሲጠይቀው ውሻውም “አህያው ልብ የለውም፡፡ ልብማ ቢኖረው ኖሮ እያናፋ አንተን ባልጠራህ ነበር፡፡” ብሎ መለሰለት፡፡
በዚህ ጊዜ ውሻው ጅቡ ሊገድለው እንደፈለገ ስለገባው መሮጥ ጀመረ፡፡ ጅቡም ውሻውን እያሳደደው ሲከተለው ውሻው አንድ እሾሃማ አጥር አጠገብ ሲደርስ እሾሁን ጠምዞ ወደ አጥሩ ውስጥ ገባ፡፡ ሰውነቱ በሙሉ ወደ አጥሩ ውስጥ ሲገባ ጅራቱ ብቻ ውጪ ስለቀረ ጅቡ ለቀም አድርጎ ቆረጠው፡፡ እሾሃማው አጥር የውሻው ጌታ ግቢ ነበር፡፡ ጅቡም በኩራት “ብታመልጠኝም ጅራትህን ቆርጨዋለሁ፡፡” አለው፡፡ ውሻው ግን በጅቡ ስቆበት “ጌታዬ የሚተኛው በቁርበት ላይ በመሆኑ እኔም አጠገቡ ነው የምተኛውና እኛ ውሾች እንደተለመደው በጅራታችን አመድ ስለምናቦን እኔም ጌታዬ ላይ አመድ እንዳላቦንበት ሰሞኑን ጅራቴን ልቆርጥ አቅጄ ስለነበረ ብዙም የጀግንነት ስሜት አይሰማህ፡፡ እኔም ልቆርጠው ነበርና፡፡” አለው ይባላል፡፡
In the original voice — hear tales from Omo Zoneኦሞ ዞን, told in an Omo Valley language. Listen ›