The Two Loversሁለቱ ፍቅረኛሞች
Amharaአማራ
Narrated by Shimelash Bequele
There is one little story being told around Bahar Dar.
There were two lovers. These two lovers went to one of the monasteries in Lake Tana1 . The name of the monastery is Dega Stephanos. They went to this monastery by a papyrus boat. A s they arrived at the monastery they left their boat at the edge of the water. And they started enjoying their love in the monastery.
In the meantime, their boat was driven away by a strong wind and people started to hunt for them, thinking that they were missing.
A lot has been said about their absence around the city. In the middle of the city, one person who knows much about them started looking for them. And he went to the same monastery in order to search for them. He saw their clothes from a distance and he got shocked. And he rushed up to them. As he arrived he found them sleeping together but dead.
As a result, that monastery is now named “The Edge of Love”.
ሁለቱ ፍቅረኛሞች
በሺመላሽ በቀለ የተተረከ
በባህር ዳር አካባቢ የሚነገር አንድ ታሪክ አለ፡፡
በአንድ ወቅት ሁለት ፍቅረኛሞች ጣና ሃይቅ1 ላይ ወደሚገኙት ገዳማት ይሄዳሉ፡፡ የአንዱ ገዳም ስም ደጋ እስጢፋኖስ ይባላል፡፡
ወደዚህም ገዳም በታንኳ ሄዱ፡፡ ከገዳሙ እንደደረሱም ታንኳቸውን ሃይቁ ዳር ትተው በገዳሙ ውስጥ ጥሩ የፍቅር ጊዜ ማሳለፍ ጀመሩ፡፡
በዚህን ጊዜ ታዲያ ታንኳቸው በማዕበል በመወሰዷ እነርሱም አብረው ጠፍተዋል በሚል ሰዎች ይፈልጓቸው ጀመር፡፡ ስለፍቅረኛሞቹ መጥፋት በከተማው ዙሪያ ብዙ ነገር ተባለ፡፡ አንድ የከተማው ሰው ስለእነርሱ ብዙ ያውቅ ነበርና ይፈልጋቸው ጀመር፡፡ ወደ ተባለውም ገዳም በመሄድ ሊያገኛቸው ሞከረ፡፡ ልብሳቸውንም ከሩቅ አይቶ ደነገጠ፡፡ እየሮጠም ወደእነርሱ ሲደርስ አብረው ተኝተው ግን ሞተው አገኛቸው፡፡
በዚህም ምክንያት ገዳሙ አሁን የፍቅር ጠርዝ እየተባለ ይጠራል፡፡
In the original voice — hear tales from Amharaአማራ, told in Amharic. Listen ›