The Dog, the Goat and the Donkeyውሻ፣ ፍየልና አህያ
Somaliaሶማሌ
Narrated by Abdul Amin Ahmed
Once there was a dog, a goat and a donkey who wanted to travel to another country. So they got on the bus. The dog had ten birr (the main unit of currency in Ethiopia). The donkey had five birr, but the goat had no money.
The bus ticket cost five birr. But when the dog gave ten birr to the conductor, he didn’t get any change. Because the goat had no money, she tried to hide herself in the bus. But the donkey paid his five birr. When the bus arrived at its destination they all got off.
The dog always runs after the bus shouting, “Give me my five birr! My five birr!” The goat runs away from the bus, saying, “The conductor will ask me for my money.” But the donkey doesn’t move. He’s already paid his five birr and he feels quite safe and happy.
ውሻ፣ ፍየልና አህያ
በአብዱል አሚን አህመድ የተተረከ
በአንድ ወቅት ውሻ፣ ፍየልና አህያ ወደ ሌላ አገር አብረው ለመሰደድ ይነሳሉ፡፡ አውቶብስ ላይም ተሳፈሩ፡፡ ውሻው አስር ብር ሲኖረው አህያዋ አምስት ብር ነበራት፡፡ ፍየሏ ግን ምንም ገንዘብ አልነበራትም፡፡
የአውቶብሱ ቲኬት ዋጋ አምስት ብር ስለነበረ ውሻው ለቲኬት ቆራጯ አስር ብር ሲሰጣት መልስ አልሰጠችውም፡፡ ፍየሏ ምንም ገንዘብ ስላልነበራት አውቶብሱ ውስጥ ተደብቃ ገባች፡፡ አህያውም የራሱን ሂሳብ አምስት ብር ከፍሎ አውቶብሱ የመጨረሻው ፌርማታ ሲደርስ ሁሉም ወረዱ፡፡
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ውሻ ሀልጊዜ አውቶብስ እየተከተለ “አምስት ብሬን አምጣ! አምስት ብሬን!” እያለ ሲሮጥ ፍየል ግን “ቲኬት ቆራጯ ገንዘብ አምጪ ትለኛለች፡፡” በማለት ከአውቶብሱ ትሸሻለች፡፡ አህያዋ ታዲያ የራሷን አምስት ብር ስለከፈለች ሁልጊዜ በመረጋጋትና በደስታ ስሜት ከአውቶብስ አትሸሽም፡፡
In the original voice — hear tales from Somaliaሶማሌ, told in Somali. Listen ›