Ethiopian Folktales

The Baboon and the Monkeyዝንጀሮና ጦጣዋ

Omo Zoneኦሞ ዞን · 1 min readደቂቃ ንባብ

Text size Share

Narrated by Zarke Goite

The baboon and the monkey were living together in olden times. Their faces were the same. But although their faces were similar, the baboon was bigger and the monkey was smaller.

One day they held a meeting and after much discussion they came to the decision that if they sat on top of each other they could reach up to the sky.

The monkey said to the baboons, “You are big and strong so you must be at the bottom of the pile and we’ll climb on top of you to build up the pile.”

So the baboons started at the bottom, one after the other and the monkeys were sitting on the ground near them. After making the pile one of the monkeys put his finger into the anus of the baboon at the very bottom of the pile, so the whole pile collapsed. The bottom baboon had leaped up, so shocked.

So the monkeys, fearing the baboons’ revenge, fled away, afraid of being beaten to death.

And so they reached a forest and prayed to God, “Oh God, we have nowhere to hide. The baboons are going to beat us to death.”

“Why should you worry?” God said to them. “I’ll change your faces and there will be no problem.”

So God created the red patches at the bottom of the baboon, not to grow any hair. And on the monkeys he put white hair on the eyebrows. Then, after that, they started living together in peace, to these days, each of them not knowing the original looks of the other.

ዝንጀሮና ጦጣዋ

በዛርኬ ጎይቴ የተተረከ

በድሮ ጊዜ ዝንጀሮና ጦጣ አብረው ይኖሩ ነበረ፡፡ ፊታቸውም ይመሳሰል ነበር፡፡ ሆኖም ፊታቸው ቢመሳሰልም ዝንጀሮ በአካል ግዙፍ ሲሆን ጦጣ ግን አነስ ያለች ነበረች፡፡

ታዲያ ከእለታት አንድ ቀን ሁለቱ ስብሰባ ከተቀመጡ በኋላ ብዙ ተወያይተው ሲያበቁ በመጨረሻ አንዱ በሌላው ላይ ቢደራረቡ ሰማይ ላይ እንደሚደርሱ ተስማሙ፡፡

ጦጣም ዝንጀሮዎችን “እናንተ በአካል ግዙፍ ስለሆናችሁ እናንተ ከስር ሆናችሁ እኛ ከላያችሁ ላይ በመሆን ወደላይ መደራረብ እንችላለን፡፡” አለች፡፡

በዚህ ዓይነት ዝንጀሮዎቹ ከስር ሆነው አንዱ በሌላው ላይ ሲደራረቡ ጦጣዎቹ አጠገባቸው መሬት ላይ ሆነው ይመለከቷቸው ነበር፡፡ እርስ በርስ ላይ ተከማምረው ሲጨርሱም አንዲቷ ጦጣ ከስር መሬት ላይ ያለውን ዝንጀሮ ፊንጢጣውን በጣቷ ብትደነቁለው ከስር ያለው ዝንጀሮ በድንጋጤ ሲዘል ክምሩ ፈረሰ፡፡

በዚህ ጊዜ ጦጣዎቹ የዝንጀሮዎቹን የበቀል እርምጃ ፈርተው ሮጠው በመሸሽ ተደብድበው ከመሞት አመለጡ፡፡ ከአንድ ጫካ አጠገብ በደረሱም ጊዜ “ጌታ ሆይ የምንሸሸግበት ቦታ የለንም፡፡ ዝንጀሮዎቹ ደብድበው ሊገድሉን ነውና አድነን፡፡” ብለው ለአምላክ ፀለዩ፡፡

ፈጣሪም “ለምን ትጨነቃላችሁ? ፊታችሁን እቀይረውና ከችግሩ ታመልጣላችሁ፡፡” ብሎ አምላክ የዝንጀሮዎቹን መቀመጫ ፀጉር እንዳያበቅል ሲመልጠው ጦጣዎቹ ቅንድብ ላይ ደግሞ ነጭ ፀጉር አደረገበት፡፡ ከዚያን ጊዜ በኋላ አንዱ የሌላኛውን የቀድሞ መልክ ስለማያውቅ እስካሁን ድረስ በሰላም አብረው ይኖራሉ፡፡

In the original voice — hear tales from Omo Zoneኦሞ ዞን, told in an Omo Valley language. Listen ›