Abba Bukkushአባ ቡኩሽ
Somaliaሶማሌ
Narrated by Yusuf Adem Mandre
A long time ago, there lived a person called Abba Bukkush. He was a jolly fellow. He used to make the king laugh very much, so the king called him Abba Bukkush, which means 'Father of Laughter'. Abba Bukkush always sat beside the king.
Then one day he said to his friend, “The king is a very good man but when one man called Afewerke made mistakes, the king didn’t punish him. He should have given him some sort of punishment.”
Abba Bukkush’s friend went to the king and told him what Abba Bukkush said.
Then the king said, “Aha, so he has started to show disrespect for me,” and he was very angry with Abba Bukkush.
He ordered three of his soldiers to go to Abba Bukkush’s house and shit on his mattress.
So the soldiers went to Abba Bukkush’s house and said, “We have been ordered to shit on your mattress.”
So they brought the mattress out of the house and started to prepare themselves to shit.
At this time Abba Bukkush brought a big stick and said, “The king has only ordered you to shit on my mattress but he has not ordered you to pee. So if I see a drop of pee on my mattress I will beat your heads with this stick.”
The soldiers were confused and frightened since they couldn’t do one without the other, so they went back to the king and told him the story.
So the king was amazed and began to laugh and ordered his soldiers to take him some gifts.
አባ ቡኩሽ
በዩሱፍ አደም ማንደሬ የተተረከ
ከብዙ ዓመታት በፊት አንድ አባ ቡኩሽ የሚባል ሰው ነበረ፡፡ በጣም ቄንጠኛ ሰው ሲሆን ንጉሱን በጣም ያስቀው ስለነበረ ንጉሱም አባ ቡኩሽ ማለትም ‘የሳቅ አባት’ ብሎ ስም አወጣለት፡፡ አባ ቡኩሽ ሁልጊዜ ከንጉሱ ጎን ነበር የሚቀመጠው፡፡
ከእለታት አንድ ቀን ታዲያ ጓደኛውን “ንጉሱ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ ነገር ግን አንድ አፈወርቅ የሚባል ሰው ስህተት ሲሰራ አልቀጣውም፡፡ አንድ ዓይነት ቅጣት ሊጥልበት ይገባ ነበር፡፡” አለው፡፡
በዚህ ጊዜ የአባ ቡኩሽ ጓደኛ ወደ ንጉሡ ዘንድ ሄዶ አባ ቡኩሽ የተናገረውን ነገር ነገረው፡፡ ንጉሡም “አሃ! በእኔ ላይ ንቀት እያደረበት ነው ማለት ነው፡፡” ብሎ በአባ ቡኩሽ በጣም ተበሳጨበት፡፡
ከዚያም ሶስት ወታደሮቹን አስጠርቶ ወደ አባ ቡኩሽ ቤት ሄደው ፍራሹ ላይ ሠገራ እንዲፀዳዱበት አዘዛቸው፡፡
ስለዚህ ወታደሮቹ በታዘዙት መሠረት ወደ አባ ቡኩሽ ቤት ሄደው “ፍራሽህ ላይ እንድንፀዳዳ ታዘናል፡፡” ብለው ነገሩት፡፡
ወታደሮቹም ፍራሹን ከቤት ውስጥ አውጥተው ሊፀዳዱበት ሲዘጋጁ አባ ቡኩሽ ትልቅ ዱላ ይዞ መጥቶ “በሉ እንግዲህ ንጉሱ ያዘዛችሁ ሰገራችሁን እንድትፀዳዱ አንጂ ሽንታችሁን እንድትሸኑ ስላልሆነ ፍራሼ ላይ አንዲት የሽንት ጠብታ ባይ ጭንቅላታችሁን በዚህ ዱላ ነው የማፈርሰው፡፡” አላቸው፡፡
ወታደሮቹም ሳይሸኑ መፀዳዳት ስለማይችሉ በጣም ግራ ስለተጋቡ ወደ ንጉሱ ተመልሰው ሄደው ስለሁኔታው ነገሩት፡፡
በዚህ ጊዜ ንጉሱ በጣም ተደንቆ በመሳቅ ወታደሮቹ ለአባ ቡኩሽ ስጦታ ይዘውለት እንዲሄዱ አዘዛቸው፡፡
In the original voice — hear tales from Somaliaሶማሌ, told in Somali. Listen ›